ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 33:25-30 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

25. በዚህ ጊዜ ሥጋው እንደ ሕፃን ልጅ ገላ ይታደሳል፤ወደ ወጣትነቱም ዘመን ይመለሳል።

26. ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል፤ ሞገስም ያገኛል፤የእግዚአብሔርን ፊት ያያል፤ ሐሤትም ያደርጋል፤እግዚአብሔር ወደ ጽድቅ ቦታው ይመልሰዋል።

27. ከዚያም ወደ ሰዎች መጥቶ እንዲህ ይላል፤‘ኀጢአትን ሠርቻለሁ፤ ትክክል የሆነውን አጣምሜአለሁ፤ነገር ግን የእጄን አላገኘሁም።

28. ነፍሴ ወደ ጒድጓድ እንዳትወርድ፣ታድጎአታል፤ በሕይወትም ሆኜ ብርሃን አያለሁ።’

29. “እግዚአብሔር ይህን ሁሉ፣ሁለት ሦስት ጊዜ ለሰው ያደርጋል።

30. ይኸውም የሕይወት ብርሃን ይበራለት ዘንድ፣ነፍሱን ከጒድጓድ ለመመለስ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 33