ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 33:19-25 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

19. ደግሞም ሰው ታሞ በዐልጋው ላይ ሳለ፣በዐጥንቱ የዘወትር ሥቃይ ይገሥጸዋል፤

20. ያኔም ሕይወቱ መብልን ትጠላለች፤ነፍሱም ምርጥ ምግብን ትጠየፋለች።

21. እንዳልነበረ ሆኖ ሥጋው ይመነምናል፤ተሸፍኖ የነበረው ዐጥንቱም ገጦ ይወጣል።

22. ነፍሱ ወደ ጒድጓድ፣ሕይወቱም ወደ ሞት መልእክተኞች ትቀርባለች።

23. “ሆኖም ትክክለኛውን መንገድ ለሰው ያመለክት ዘንድ፣መካከለኛም ይሆንለት ዘንድ፣ከሺህ አንድ መልአክ ቢገኝ፣

24. ለሰውየውም በመራራት፣‘ቤዛ አግኝቼለታለሁና፣ወደ ጒድጓድ እንዳይወርድ አድነው’ ቢለው፣

25. በዚህ ጊዜ ሥጋው እንደ ሕፃን ልጅ ገላ ይታደሳል፤ወደ ወጣትነቱም ዘመን ይመለሳል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 33