ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 33:14-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. ሰው ባያስተውለውም፣እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፤

15. ሰዎች ዐልጋቸው ላይ ተኝተው ሳሉ፣ከባድ እንቅልፍ ሲወድቅባቸው፣በሕልም፣ በሌሊትም ራእይ፣ ይናገራል።

16. በጆሯቸው ይናገራል፤በማስጠንቀቂያም ያስደነግጣቸዋል፤

17. ሰውን ከክፉ ሥራው ይመልሳል፤ከትዕቢት ይጠብቃል፤

18. ነፍሱን ከጒድጓድ፤ሕይወቱንም ከሰይፍ ጥፋት ያድናል።

19. ደግሞም ሰው ታሞ በዐልጋው ላይ ሳለ፣በዐጥንቱ የዘወትር ሥቃይ ይገሥጸዋል፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 33