ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 22:2-18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. “ሰው እግዚአብሔርን ሊጠቅም ይችላልን?ጠቢብ እንኳ ቢሆን ምን ይጠቅመዋል?

3. አንተ ጻድቅ ብትሆን ሁሉን የሚችለውን አምላክ ምን ደስ ታሰኘዋለህ?መንገድህ ያለ ነቀፋ ቢሆንስ የሚተርፈው ምንድን ነው?

4. “እርሱ የሚገሥጽህ፣ፍርድ ቤትም የሚያቀርብህ ስለምትፈራው ነውን?

5. ክፋትህ ታላቅ፣ኀጢአትህ ፍጻሜ የሌለው አይደለምን?

6. ያለ አንዳች ምክንያት ከወንድሞችህ መያዣ ወስደሃል፤ሰዎችን ገፈህ፣ ያለ ልብስ ዕራቍታቸውን አስቀርተሃል።

7. የዛሉትን ውሃ አላጠጣህም፤የተራቡትንም ምግብ ከልክለሃል።

8. ባለ ርስትና ኀያል፣በእርሱም የምትኖር ክቡር ሰው ብትሆንም፣

9. መበለቶችን ባዶ እጃቸውን ሰደሃል፤የድኻ ዐደጎችንም ክንድ ሰብረሃል።

10. ድንገተኛ አደጋ ያናወጠህ፤ወጥመድም ዙሪያህን የከበበህ ለዚህ ነው።

11. እንዳታይ ጨለማ የሆነብህ፣ጐርፍም ያጥለቀለቀህ ለዚህ ነው።

12. “እግዚአብሔር ከፍ ባለው ሰማይ የሚኖር አይደለምን?በሩቅ ከፍታ ያሉትን ከዋክብት ያያል!

13. ይህም ሆኖ ሳለ እንዲህ አልህ፤ ‘እግዚአብሔር ምን ያውቃል?በእንዲህ ያለ ጨለማ ውስጥስ ይፈርዳልን?

14. በሰማይ ክበብ ላይ ሲራመድ፣እንዳያየን ጥቅጥቅ ያለ ደመና ይሸፍነዋል።’

15. ኀጢአተኞች በሄዱባት፣በጥንቷ መንገድ እንደ ተመላለስህ ትቀራለህን?

16. ጊዜያቸው ሳይደርስ ተነጠቁ፤መሠረታቸውም በጐርፍ ተወሰደ።

17. እግዚአብሔርንም ‘አትድረስብን!ሁሉን የሚችል አምላክም ምን ያደርግልናል?’ አሉ።

18. ቤታቸውን በመልካም ነገር የሞላው ግን እርሱ ነው፤ስለዚህ ከኀጢአተኞች ምድር እርቃለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 22