ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 15:23-35 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

23. የአሞራ እራት ለመሆን ይቅበዘበዛል፤የጨለማ ቀን መቅረቡን ያውቃል።

24. ጭንቀትና ሐዘን ያስፈራሩታል፤ለማጥቃት እንደ ተዘጋጀ ንጉሥም ያይሉበታል፤

25. እጁን በእግዚአብሔር ላይ አንሥቶአልና፤ሁሉን የሚችለውን አምላክም ደፍሮአል፤

26. ወፍራምና ጠንካራ ጋሻ አንግቦ፣ሊቋቋመው ወጥቶአል።

27. “ፊቱ በስብ ቢሸፈን፣ሽንጡ በሥጋ ቢደነድንም፣

28. መኖሪያው በፈራረሱ ከተሞች፣የፍርስራሽ ክምር ለመሆን በተቃረቡ፣ሰው በማይኖርባቸው ወና ቤቶች ውስጥ ይሆናል።

29. ከእንግዲህ ባለጠጋ አይሆንም፤ ሀብቱም አይቈይም፤ይዞታውም በምድር ላይ አይሰፋም።

30. ከጨለማ አያመልጥም፤ቅርንጫፎቹን ነበልባል ያደርቃቸዋል፤በእግዚአብሔርም እስትንፋስ ይወሰዳል።

31. በአጸፋው አንዳች አያገኝምና፤ከንቱን ነገር በመታመን ራሱን አያታልል።

32. ጊዜው ሳይደርስ ይጠወልጋል፤ቅርንጫፉም አይለመልምም።

33. ፍሬው በጮርቃነት እንደ ተለቀመበት የወይን ተክል፤አበባውም እንደ ረገፈበት የወይራ ዛፍ ይሆናል።

34. የዐመፀኞች ጉባኤ ትመክናለች፤የጉቦ ሱሰኞችም ድንኳን በእሳት ትበላለች።

35. መከራን ይፀንሳሉ፣ ክፋትንም ይወልዳሉ፤በሆዳቸውም ተንኰል ይጠነስሳሉ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 15