ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 15:18-31 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

18. ጠቢባን ከአባቶቻቸው የተቀበሉትን፤ሳይሸሽጉ የተናገሩትን አስረዳሃለሁ፤

19. ምድሪቱ ለአባቶቻቸው ተሰጠች፤በመካከላቸውም ባዕድ አልተቀመጠም፤

20. ክፉ ሰው ዕድሜውን ሙሉ፣ጨካኙም በተመደበለት ዘመን ሁሉ ይሠቃያል።

21. የሚያስደነግጥ ድምፅ በጆሮው ላይ ይጮኻል፤በሰላም ጊዜ ቀማኞች አደጋ ያደርሱበታል።

22. ከጨለማ ወጥቶ ማምለጥ ይፈራል፤ለሰይፍም የተመደበ ነው።

23. የአሞራ እራት ለመሆን ይቅበዘበዛል፤የጨለማ ቀን መቅረቡን ያውቃል።

24. ጭንቀትና ሐዘን ያስፈራሩታል፤ለማጥቃት እንደ ተዘጋጀ ንጉሥም ያይሉበታል፤

25. እጁን በእግዚአብሔር ላይ አንሥቶአልና፤ሁሉን የሚችለውን አምላክም ደፍሮአል፤

26. ወፍራምና ጠንካራ ጋሻ አንግቦ፣ሊቋቋመው ወጥቶአል።

27. “ፊቱ በስብ ቢሸፈን፣ሽንጡ በሥጋ ቢደነድንም፣

28. መኖሪያው በፈራረሱ ከተሞች፣የፍርስራሽ ክምር ለመሆን በተቃረቡ፣ሰው በማይኖርባቸው ወና ቤቶች ውስጥ ይሆናል።

29. ከእንግዲህ ባለጠጋ አይሆንም፤ ሀብቱም አይቈይም፤ይዞታውም በምድር ላይ አይሰፋም።

30. ከጨለማ አያመልጥም፤ቅርንጫፎቹን ነበልባል ያደርቃቸዋል፤በእግዚአብሔርም እስትንፋስ ይወሰዳል።

31. በአጸፋው አንዳች አያገኝምና፤ከንቱን ነገር በመታመን ራሱን አያታልል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 15