ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 15:1-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ቴማናዊው ኤልፋዝ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2. “ጠቢብ ሰው በከንቱ ንግግር መልስ ይሰጣልን?ወይስ በምሥራቅ ነፋስ ሆዱን ይሞላል?

3. በማይረባ ቃል፣ፍሬ ቢስ በሆነም ንግግር ይከራከራልን?

4. አንተ ግን እግዚአብሔርን መፍራት ታጣጥላለህ፤አምልኮተ እግዚአብሔርን ትከለክላለህ።

5. ኀጢአትህ አፍህን ታስተምረዋለች፤የተንኰለኞችንም አነጋገር መርጠህ ትይዛለህ።

6. የሚፈርድብህ አንደበትህ እንጂ እኔ አይደለሁም፣የሚመሰክርብህም እኔ ሳልሆን የገዛ ከንፈርህ ነው።

7. “ለመሆኑ ከሰው ሁሉ ቀድመህ የተወለድህ አንተ ነህን?ወይስ ከኰረብቶች በፊት ተገኝተሃል?

8. በእግዚአብሔር የመማክርት ጉባኤ ላይ ነበርህን?ጥበብስ የተሰጠው ለአንተ ብቻ ነው?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 15