ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 14:12-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. እንደዚሁም ሰው ይተኛል ቀናም አይልም፤ሰማይ እስከሚያልፍ ድረስ አይነቃም፤ከእንቅልፉም አይነሣም።

13. “ምነው መቃብር ውስጥ በሰወርኸኝ!ቍጣህም እስከሚያልፍ በሸሸግኸኝ!ምነው ቀጠሮ ሰጥተህ፣ከዚያ በኋላ ባስታወስኸኝ!

14. ሰው ከሞተ በኋላ ተመልሶ በሕይወት ይኖራል?እድሳቴ እስከሚመጣ ድረስ፣ተጋድሎ የሞላበትን ዘመኔን ሁሉ እታገሣለሁ።

15. ትጠራኛለህ፤ እኔም እመልስልሃለሁ፤የእጅህንም ሥራ ትናፍቃለህ።

16. በዚያን ጊዜ በእርግጥ እርምጃዬን ትከታተላለህ፤ነገር ግን ኀጢአቴን አትቈጣጠርም።

17. መተላለፌ በከረጢት ይቋጠራል፤ኀጢአቴንም ትሸፍናለህ።

18. “ተራራ እንደሚሸረሸርና እንደሚወድቅ፣ዐለትም ከስፍራው እንደሚወገድ፣

19. ውሃ ድንጋይን እንደሚቦረቡር፣ጐርፍም ዐፈርን አጥቦ እንደሚወስድ፣አንተም የሰውን ተስፋ ታጠፋለህ።

20. አንድ ጊዜ ፈጽመህ ትበረታለህ፤ እርሱም ያልፋል፤ገጽታውን ትቀይራለህ፤ ትሸኘዋለህም።

21. ልጆቹ ቢከበሩ አያውቅም፤ቢዋረዱም አያይም።

22. የገዛ አካሉ ሕመም ብቻ ይሰማዋል፤ለራሱም ብቻ ያለቅሳል።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 14