ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 12:8-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ለምድር ተናገሩ፤ ታስተምራችኋለች፤የባሕርም ዓሣ ይነግራችኋል።

9. የእግዚአብሔር እጅ ይህን እንዳደረገ፣ከእነዚህ ሁሉ የማያውቅ ማን ነው?

10. የፍጥረት ሁሉ ሕይወት፣የሰውም ሁሉ መንፈስ በእጁ ናትና፤

11. ምላስ የምግብን ጣዕም እንደሚለይ፣ጆሮ ቃላትን አይለይምን?

12. ጥበብ ያለው በአረጋውያን ዘንድ አይደለምን?ማስተዋልስ ረጅም ዕድሜ ባላቸው ዘንድ አይገኝምን?

13. “ጥበብና ኀይል የእግዚአብሔር ናቸው፤ምክርና ማስተዋልም በእርሱ ዘንድ ይገኛሉ።

14. እርሱ ያፈረሰውን መልሶ የሚገነባ የለም፣እርሱ ያሰረውን የሚፈታ አይገኝም።

15. እርሱ ውሃን ቢከለክል፣ ድርቅ ይሆናል፤ቢለቀውም ውሃው ምድሪቱን ያጥለቀልቃል።

16. ብርታትና ድል ማድረግ በእርሱ ዘንድ ይገኛል፤አታላዩም ተታላዩም በእርሱ እጅ ናቸው።

17. አማካሪዎችን ከጥበባቸው ያራቍታል፤ፈራጆችንም ማስተዋል ይነሣል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 12