ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 11:12-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. ጅል ሰው ጥበበኛ ከሚሆን ይልቅ፣የሜዳ አህያ ሰው ሆኖ ቢወለድ ይቀላል።

13. “ነገር ግን ልብህን ብትሰጠው፣እጅህንም ወደ እርሱ ብትዘረጋ፣

14. በእጅህ ያለውን ኀጢአት ብታርቅ፣ክፋትም በድንኳንህ እንዳይኖር ብታደርግ፣

15. በዚያን ጊዜ ሳታፍር ቀና ትላለህ፤ያለ ፍርሀት ጸንተህ ትቆማለህ፤

16. መከራህን ትረሳለህ፤ዐልፎ እንደሄደ ጐርፍም ታስበዋለህ።

17. ሕይወትህ ከቀትር ይልቅ ያበራል፤ጨለማውም እንደ ንጋት ይሆናል።

18. ተስፋ ስላለ ተደላድለህ ትቀመጣለህ፤ዙሪያህን ትመለከታለህ፤ በሰላምም ታርፋለህ።

19. ያለ አንዳች ሥጋት ትተኛለህ፤ብዙ ሰዎችም ደጅ ይጠኑሃል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 11