ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 3:1-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በዚያ ዘመን፣ በዚያ ጊዜ፣የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ምርኮ ስመልስ፣

2. አሕዛብን ሁሉ እሰበስባለሁ፤ወደ ኢዮሣፍጥም ሸለቆ አወርዳቸዋለሁ፤ስለ ርስቴ፣ ስለ ሕዝቤ፣ ስለ እስራኤል፣በዚያ ልፈርድባቸው እገባለሁ፤ምድሬን ከፋፍለዋል፤ሕዝቤንም በሕዝቦች መካከል በታትነዋልና።

3. በሕዝቤ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ፤ወንዶች ልጆችን በዝሙት አዳሪዎች ለወጡ፤ወይን ጠጅ ለመጠጣትም፣ሴቶች ልጆችን ሸጡ።

4. “ጢሮስና ሲዶና እንዲሁም እናንተ የፍልስጥኤም ግዛቶች ሁሉ ሆይ፤ እንግዲህ በእኔ ላይ ምን አላችሁ? ስላደረግሁት ነገር ብድር ልትመልሱልኝ ነውን? የምትመልሱልኝ ከሆነ፣ በፍጥነትና በችኰላ እናንተ ያደረጋችሁትን በራሳችሁ ላይ መልሼ አደርግባችኋለሁ።

5. ብሬንና ወርቄን ወስዳችኋል፤ የተመረጠውንም ንብረቴን ተሸክማችሁ ወደ ቤተ መቅደሳችሁ አስገብታችኋልና።

6. ከገዛ ምድራቸው ልታርቋቸው፣ የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ሰዎች ለግሪኮች ሸጣችኋቸው።

7. “እነሆ፤ እነርሱን ከሸጣችሁባቸው ቦታዎች አነሣሣቸዋለሁ፤ እናንተም ያደረጋችሁትን በገዛ ራሳችሁ ላይ እመልስባችኋለሁ።

8. ወንዶችንና ሴቶች ልጆቻችሁን ለይሁዳ ሰዎች ሸጣለሁ፤ እነርሱም መልሰው በሩቅ ላሉት ለሳባ ሰዎች ይሸጧቸዋል፤” እግዚአብሔር ይህን ተናግሮአልና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 3