ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 2:28-32 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

28. “ከዚህም በኋላ፣መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈሳለሁ፤ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤ሽማግሌዎቻችሁ ሕልም ያልማሉ፤ጒልማሶቻችሁም ራእይ ያያሉ።

29. በእነዚያ ቀናት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎች ላይ እንኳ፣መንፈሴን አፈሳለሁ።

30. ድንቆችን በሰማያት፣እንዲሁም በምድር፣ደምና እሳት፣ የጢስም ዐምድ አሳያለሁ።

31. ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ከመምጣቱ በፊት፣ፀሓይ ትጨልማለች፤ጨረቃም ወደ ደም ትለወጣለች።

32. የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ፣እርሱ ይድናል፤ እግዚአብሔርም እንዳለው፣በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም፣መድኀኒት ይገኛል፤ከትሩፋኑም መካከል እግዚአብሔር የጠራቸው በዚያ ይገኛሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 2