ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 2:24-29 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

24. ዐውድማዎቹ በእህል ይሞላሉ፤መጥመቂያ ጒድጓዶችም፣ በአዲስ የወይን ጠጅና በዘይት ተሞልተው ያፈሳሉ።

25. “በመካከላችሁ የሰደድሁት ታላቁ ሰራዊት፣ትልልቁ አንበጣና ትንንሹ አንበጣ፣ሌሎች አንበጦችና የአንበጣው መንጋ የበላውን፣እነዚህ ሁሉ የበሏቸውን ዓመታት ዋጋ እመልስላችኋለሁ።

26. እስክትጠግቡ የምትበሉት ብዙ ምግብ ይኖራችኋል፤ድንቅ ነገሮችን ለእናንተ የሠራውን፣የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ስም ታመሰግናላችሁ፤ሕዝቤም ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም።

27. ከዚያም እኔ በእስራኤል መካከል እንዳለሁ፣እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር እንደሆንሁ፣እንደ እኔም ያለ፣ ሌላ እንደሌለ ታውቃላችሁ፤ሕዝቤም ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም።

28. “ከዚህም በኋላ፣መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈሳለሁ፤ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤ሽማግሌዎቻችሁ ሕልም ያልማሉ፤ጒልማሶቻችሁም ራእይ ያያሉ።

29. በእነዚያ ቀናት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎች ላይ እንኳ፣መንፈሴን አፈሳለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 2