ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 2:20-32 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. “የሰሜንን ሰራዊት ከእናንተ አርቃለሁ፤ፊቱን ወደ ምሥራቁ ባሕር፣ጀርባውንም ወደ ምዕራቡ ባሕር በማድረግ፣ወደ ደረቀውና ወደ ባድማው ምድር እገፋዋለሁ፤ግማቱ ይወጣል፤ክርፋቱም ይነሣል።”በእርግጥ እርሱ ታላቅ ነገር አድርጎአል።

21. ምድር ሆይ፤ አትፍሪ፤ደስ ይበልሽ፤ ሐሤትም አድርጊ፤በእርግጥ እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አድርጎአል።

22. የዱር እንስሳት ሆይ፤ አትፍሩ፤መሰማሪያ መስኮቹ ለምልመዋልና፤ዛፎቹ ፍሬያቸውን አፍርተዋል፤የበለሱ ዛፍና የወይኑ ተክልም እጅግ አፍርተዋል።

23. የጽዮን ሰዎች ሆይ፤ ደስ ይበላችሁ፤በአምላካችሁ በእግዚአብሔር፣ ሐሤት አድርጉ፤የበልግን ዝናብ፣በጽድቅ ሰጥቶአችኋልና፤እንደ ቀድሞውም፣የበልግንና የጸደይን ዝናብ በብዛት ልኮላችኋል።

24. ዐውድማዎቹ በእህል ይሞላሉ፤መጥመቂያ ጒድጓዶችም፣ በአዲስ የወይን ጠጅና በዘይት ተሞልተው ያፈሳሉ።

25. “በመካከላችሁ የሰደድሁት ታላቁ ሰራዊት፣ትልልቁ አንበጣና ትንንሹ አንበጣ፣ሌሎች አንበጦችና የአንበጣው መንጋ የበላውን፣እነዚህ ሁሉ የበሏቸውን ዓመታት ዋጋ እመልስላችኋለሁ።

26. እስክትጠግቡ የምትበሉት ብዙ ምግብ ይኖራችኋል፤ድንቅ ነገሮችን ለእናንተ የሠራውን፣የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ስም ታመሰግናላችሁ፤ሕዝቤም ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም።

27. ከዚያም እኔ በእስራኤል መካከል እንዳለሁ፣እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር እንደሆንሁ፣እንደ እኔም ያለ፣ ሌላ እንደሌለ ታውቃላችሁ፤ሕዝቤም ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም።

28. “ከዚህም በኋላ፣መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈሳለሁ፤ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤ሽማግሌዎቻችሁ ሕልም ያልማሉ፤ጒልማሶቻችሁም ራእይ ያያሉ።

29. በእነዚያ ቀናት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎች ላይ እንኳ፣መንፈሴን አፈሳለሁ።

30. ድንቆችን በሰማያት፣እንዲሁም በምድር፣ደምና እሳት፣ የጢስም ዐምድ አሳያለሁ።

31. ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ከመምጣቱ በፊት፣ፀሓይ ትጨልማለች፤ጨረቃም ወደ ደም ትለወጣለች።

32. የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ፣እርሱ ይድናል፤ እግዚአብሔርም እንዳለው፣በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም፣መድኀኒት ይገኛል፤ከትሩፋኑም መካከል እግዚአብሔር የጠራቸው በዚያ ይገኛሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 2