ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 2:14-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. በምሕረቱ ተመልሶ፣ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር የሚሆነውን፣የእህል ቊርባንና የመጠጥ ቊርባን እንዲተርፋችሁ፣በረከቱን ይሰጣችሁ እንደሆነ ማን ያውቃል?

15. በጽዮን መለከትን ንፉ፤ቅዱስ ጾምን ዐውጁ፤የተቀደሰን ጉባኤ ጥሩ።

16. ሕዝቡን ሰብስቡ፤ጉባኤውን ቀድሱ፤ሽማግሌዎችን በአንድነት አቅርቡ፤ሕፃናትን ሰብስቡ፤ጡት የሚጠቡትንም አታስቀሩ፤ሙሽራው እልፍኙን ይተው፣ሙሽሪትም የጫጒላ ቤቷን ትተው።

17. በእግዚአብሔር ፊት የሚያገለግሉ ካህናት፣በመሠዊያውና በቤተ መቅደሱ አደባባይ መካከል ሆነው ያልቅሱ፤እንዲህም ይበሉ፤ “እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አድን፤ርስትህን በአሕዛብ መካከል መተረቻ፣መሣቂያና መሣለቂያም አታድርግ፤ለምንስ በሕዝቦች መካከል፣‘አምላካቸው ወዴት ነው?’ ይበሉን።”

18. እነሆ፤ እግዚአብሔር ስለ ምድሩ ይቀናል፤ስለ ሕዝቡም ይራራል።

19. እግዚአብሔርም እንዲህ ሲል ይመልስላቸዋል፤“እህል፣ አዲስ የወይን ጠጅና ዘይት፣እስክትጠግቡ ድረስ እሰጣችኋለሁ፤የሕዝቦች መዘባበቻ አላደርጋችሁም።

20. “የሰሜንን ሰራዊት ከእናንተ አርቃለሁ፤ፊቱን ወደ ምሥራቁ ባሕር፣ጀርባውንም ወደ ምዕራቡ ባሕር በማድረግ፣ወደ ደረቀውና ወደ ባድማው ምድር እገፋዋለሁ፤ግማቱ ይወጣል፤ክርፋቱም ይነሣል።”በእርግጥ እርሱ ታላቅ ነገር አድርጎአል።

21. ምድር ሆይ፤ አትፍሪ፤ደስ ይበልሽ፤ ሐሤትም አድርጊ፤በእርግጥ እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አድርጎአል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 2