ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 62:5-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ጐልማሳ ድንግሊቱን እንደሚያገባ፣ልጆችሽ እንዲሁ ያገቡሻል፤ሙሽራ በሙሽራዪቱ ደስ እንደሚለው፣አምላክሽም በአንቺ ደስ ይለዋል።

6. ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ዘብ ጠባቂዎችን በቅጥሮችሽ ላይ አቁሜአለሁ፤ቀንም ሆነ ሌሊት ፈጽሞ አይታክቱም።እናንት ወደ እግዚአብሔር አቤት፣ አቤት የምትሉ፤ፈጽሞ አትረፉ፤

7. ኢየሩሳሌምን እስኪያጸናት፣የምድርም ምስጋና እስኪያደርጋት ዕረፍት አትስጡት።

8. እግዚአብሔር በቀኝ እጁ፣በኀያል ክንዱም እንዲህ ሲል ምሎአል፤“ከእንግዲህ እህልሽን፣ለጠላቶችሽ መብል እንዲሆን አልሰጥም፤ከእንግዲህ የደከምሽበትን፣አዲስ የወይን ጠጅ ባዕዳን አይጠጡትም።

9. ነገር ግን መከሩን የሰበሰቡ ይበሉታል፤ እግዚአብሔርንም ያመሰግናሉ፤የወይኑን ፍሬ የለቀሙም በመቅደሴአደባባዮች ይጠጡታል።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 62