ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 57:7-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ዐልጋሽን ከፍ ባለውና በረጅሙ ኰረብታ ላይ አነጠፍሽ፤በዚያም መሥዋዕትሽን ልታቀርቢ ወጣሽ።

8. ከመዝጊያሽና ከመቃንሽ ጀርባ፣የጣዖት ምስሎችሽን ሰቀልሽ፤እኔን ትተሽ መኝታሽን ገላለጥሽ፤በላይም ወጥተሽ በጣም ገለጥሽው፤መኝታቸውን ከወደድሽላቸው ጋር ስምምነት አደረግሽ፤ዕርቃናቸውንም አየሽ።

9. የወይራ ዘይት ይዘሽ፣ሽቶ በላዩ ጨምረሽ ወደ ሞሎክ ሄድሽ፤መልእክተኞችሽን ወደ ሩቅ አገር ላክሽ፤እስከ ራሱ እስከ ሲኦልም ዘለቅሽ።

10. በመንገድ ብዛት ደከምሽ፤ነገር ግን ‘ተስፋ የለውም’ አላልሽም፤የጒልበት መታደስ አገኘሽ፤ስለዚህም አልዛልሽም።

11. “እኔን የዋሸሽኝ፤ማንን ፈርተሽ፣ ማንንስ ሠግተሽ ነው?እኔን ያላስታወስሽው፣ይህንንም በልብሽ ያላኖርሽው፣እኔን ያልፈራሽው፣ዝም ስላልሁ አይደለምን?

12. ጽድቅሽንና ሥራሽን አጋልጣለሁ፤እነርሱም አይጠቅሙሽም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 57