ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 57:1-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ጻድቅ ይሞታል፤ይህን ግን ማንም ልብ አይልም፤ ለእግዚአብሔር ያደሩ ሰዎች ይወሰዳሉ፤ጻድቃን ከክፉ ይድኑ ዘንድ፣መወሰዳቸውን፣ማንም አያስተውልም።

2. በቅንነት የሚሄዱ፣ሰላም ይሆንላቸዋል፤መኝታቸው ላይ ያርፋሉ።

3. “እናንት የአስማተኛዪቱ ልጆች ግን፣እናንት የአመንዝራውና የጋለሞታዪቱ ዘር፤ እናንት፣ ወዲህ ኑ፤

4. የምትሣለቁት በማን ላይ ነው?የምታሽሟጥጡት ማንን ነው?ምላሳችሁንስ አውጥታችሁ የምታሾፉት በማን ላይ ነው?እናንት የዐመፀኞች ልጆች፣የሐሰተኞች ዘር አይደላችሁምን?

5. በባሉጥ ዛፎች መካከል፣ቅጠሉ በተንዠረገገ ዛፍ ሥር በዝሙት የምትቃጠሉ፣በሸለቆዎች፣ በዐለት ስንጣቂዎችም ውስጥልጆቻችሁን የምትሠዉ አይደላችሁምን?

6. በሸለቆው በሚገኙት ለስላሳ ድንጋዮችውስጥ ያሉት ጣዖቶች የአንቺ ናቸው፤እነርሱም ዕጣ ፈንታዎችሽ ናቸው፤ርግጥ ነው፣ በእነርሱ ላይ የመጠጥ ቊርባን አፍስሰሻል፤የእህል ቍርባንም አቅርበሻል፤ታዲያ፣ ስለ እነዚህ ነገሮች ዝም እላለሁን?

7. ዐልጋሽን ከፍ ባለውና በረጅሙ ኰረብታ ላይ አነጠፍሽ፤በዚያም መሥዋዕትሽን ልታቀርቢ ወጣሽ።

8. ከመዝጊያሽና ከመቃንሽ ጀርባ፣የጣዖት ምስሎችሽን ሰቀልሽ፤እኔን ትተሽ መኝታሽን ገላለጥሽ፤በላይም ወጥተሽ በጣም ገለጥሽው፤መኝታቸውን ከወደድሽላቸው ጋር ስምምነት አደረግሽ፤ዕርቃናቸውንም አየሽ።

9. የወይራ ዘይት ይዘሽ፣ሽቶ በላዩ ጨምረሽ ወደ ሞሎክ ሄድሽ፤መልእክተኞችሽን ወደ ሩቅ አገር ላክሽ፤እስከ ራሱ እስከ ሲኦልም ዘለቅሽ።

10. በመንገድ ብዛት ደከምሽ፤ነገር ግን ‘ተስፋ የለውም’ አላልሽም፤የጒልበት መታደስ አገኘሽ፤ስለዚህም አልዛልሽም።

11. “እኔን የዋሸሽኝ፤ማንን ፈርተሽ፣ ማንንስ ሠግተሽ ነው?እኔን ያላስታወስሽው፣ይህንንም በልብሽ ያላኖርሽው፣እኔን ያልፈራሽው፣ዝም ስላልሁ አይደለምን?

12. ጽድቅሽንና ሥራሽን አጋልጣለሁ፤እነርሱም አይጠቅሙሽም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 57