ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 43:12-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. ገልጫለሁ፤ አድኛለሁ፤ ተናግሬአለሁ፤በመካከላችሁ እኔ እንጂ ባዕድ አምላክ አልነበረም።እኔ አምላክ እንደሆንሁ፣ እናንተ ምስክሮቼ ናችሁ” ይላል እግዚአብሔር፤

13. “ከጥንት ጀምሮ እኔው ነኝ፤ከእጄም ማውጣት የሚችል የለም፤እኔ የምሠራውን ማን ማገድ ይችላል?”

14. የእስራኤል ቅዱስ፣የሚቤዣችሁ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ስለ እናንተ በባቢሎን ላይ ሰራዊት እሰዳለሁ፤በሚመኩባቸውም መርከቦች፣ባቢሎናውያንን ሁሉ እንደ ኰብላይ አመጣለሁ።

15. እኔ እግዚአብሔር፣ የእናንተ ቅዱስ፣የእስራኤል ፈጣሪ፣ ንጉሣችሁ ነኝ።”

16. በባሕር ውስጥ መንገድ፣በማዕበል ውስጥ መተላለፊያ ያበጀ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

17. እንደ ገና ላይነሡ እዚያው እንዲተኙ፣እንደ ጧፍ ኵስታሪ ረግፈው እንዲጠፉ፣ሠረገሎችንና ፈረሶችን፣ሰራዊቱንና ደጀኑን በአንድነት ያወጣ እንዲህ ይላል፤

18. “የቀደመውን ነገር አታስቡ፤ያለፈውን እርሱ።

19. እነሆ፤ አዲስ ነገር አደርጋለሁ፤እርሱም አሁን ይበቅላል፤ አታስተውሉትምን?በምድረ በዳም መንገድ አዘጋጃለሁ፤በበረሓም ምንጭ አፈልቃለሁ፤

20. የምድረ በዳ አራዊት፣ቀበሮና ጒጒት ያከብሩኛል፤በምድረ በዳ ውሃ፣በበረሓም ምንጭ እሰጣለሁና።ለመረጥሁት ሕዝቤ ውሃ እሰጣለሁ፤

21. ለራሴ ያበጀሁት ሕዝብምስጋናዬን ያውጅ ዘንድ ይህን አደርጋለሁ።

22. “ያዕቆብ ሆይ፤ አንተ ግን አልጠራኸኝም፤እስራኤል ሆይ፤ የእኔ ነገር ታክቶሃል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 43