ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 35:6-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. አንካሳ እንደ ሚዳቋ ይዘላል፤የድዳውም አንደበት በደስታ ይዘምራል፤ውሃ ከበረሓ ይወጣል፤ምንጮችም ከምድረ በዳ ይፈልቃሉ።

7. ንዳዳማው ምድር ኵሬ ይሆናል፤የተጠማው መሬት ውሃ ያመነጫል።ቀበሮዎች በተኙባቸው ጒድጓዶች፣ሣር፣ ሸምበቆና ደንገል ይበቅልበታል።

8. በዚያ አውራ ጐዳና ይሆናል፤“የተቀደሰ መንገድ” ተብሎ ይጠራል።የረከሱ አይሄዱበትም፤በመንገዱ ላይ ላሉት ብቻ ይሆናል።ገራገሮችም ከመንገዱ አይስቱም።

9. አንበሳ አይኖርበትም፤ነጣቂ አውሬም አይወጣበትም፤እነዚህማ በዚያ ስፍራ አይገኙም፤የዳኑት ብቻ በዚያ ይሄዳሉ፤

10. እግዚአብሔር የዋጃቸው ይመለሳሉ።እየዘመሩ ወደ ጽዮን ይገባሉ፤ዘላለማዊ ደስታን እንደ አክሊል ይቀዳጁታል፤ፍሥሓና ሐሤት ያገኛሉ፤ሐዘንና ትካዜ ከዚያ ይሸሻሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 35