ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 34:3-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ከእነርሱም የተገደሉት ወደ ውጭ ይጣላሉ፤ሬሳቸው ይከረፋል፤ተራሮችም ደም በደም ይሆናሉ።

4. የሰማይ ከዋክብት ሁሉ ይሟሽሻሉ፤ሰማይ እንደ ብራና ይጠቀለላል፤የከዋክብት ሰራዊት ሁሉ፣ጠውልጎ እንደ ረገፈ የወይን ቅጠል፣ደርቆም እንደ ወደቀ የበለስ ቅጠል ይሆናሉ።

5. ሰይፌ በሰማያት እስኪበቃት ጠጥታለች፤እነሆ፤ ወደ ኤዶም፣ፈጽሞ ወዳጠፋሁት ሕዝብ ለፍርድ ወርዳለች።

6. የእግዚአብሔር ሰይፍ በደም ተነክራለች፤ሥብ ጠግባለች፤በበግ ጠቦትና በፍየል ደም፣በአውራም በግ ኵላሊት ሥብ ተሸፍናለች። እግዚአብሔር በባሶራ ከተማ መሥዋዕት፣በኤዶምም ታላቅ ዕርድ አዘጋጅቶአልና።

7. ጐሽ አብሮአቸው፣ኮርማም ከወይፈን ጋር ይወድቃል፤ምድራቸው በደም ትርሳለች፤ዐፈራቸውም ሥብ በሥብ ይሆናል።

8. እግዚአብሔር የበቀል ቀን፣ስለ ጽዮንም የሚሟገትበት ዓመት አለውና።

9. የኤዶም ምንጮች ሬንጅ፣ዐፈሯ የሚቃጠል ድኝ፣ምድሯም የሚንበለበል ዝፍት ይሆናል።

10. እሳቷ ሌሊትና ቀን አይጠፋም፤ጢሷም ለዘላለም ይትጐለጐላል፤ከትውልድ እስከ ትውልድ ባድማ ትሆናለች፤ማንም በዚያ ዳግም አያልፍም።

11. ጭልፊትና ጃርት ይወርሷታል፤ጒጒትና ቍራም ጐጆ ይሠሩባታል።እግዚአብሔር በኤዶም ላይ፣የመፈራረሷን ገመድ፣የመጥፊያዋንም ቱንቢ ይዘረጋል።

12. መሳፍንቷም መንግሥት ተብለው ለመጠራት የሚያስችላቸው ነገር አይኖራቸውም፤አለቆቿም በሙሉ ጥርግ ብለው ይጠፋሉ።

13. በቅጥር የተመሸጉ ከተሞቿን እሾኽ፣ምሽጎቹንም ሳማና አሜከላ ይወርሷቸዋል፤የቀበሮዎች ጒድጓድ፣የጒጒቶችም መኖሪያ ትሆናለች።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 34