ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 22:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ስለ ራእይ ሸለቆ የተነገረ ንግር፤እስቲ ምን ቢጨንቃችሁ ነው፤ሁላችሁም ሰገነት ላይ የወጣችሁት?

2. አንቺ ጫጫታ የሞላብሽ ከተማ፤የውካታና የፈንጠዝያ ከተማ ሆይ፤የተገደሉብሽ በሰይፍ የተሠዉ አይደሉም፤በጦርነትም አልሞቱም።

3. መሪዎችሽ በሙሉ በአንድ ላይ ሸሽተዋል፤ቀስት እንኳ ሳያነሡ ተማርከዋል፤ጠላት ገና በሩቅ ሳለ የሸሻችሁ ሁሉ፣ተይዛችሁ በአንድነት ታስራችኋል።

4. ስለዚህ፣ “ከእኔ ራቁ፤አምርሬ ላልቅስበት፣ስለ ሕዝቤ ጥፋት፣ልታጽናኑኝ አትሞክሩ” አልሁ።

5. እግዚአብሔር የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርበራእይ ሸለቆ፣የመጯጯኺያ የመረገጥና የሽብር፣ቅጥሮችን የማፈራረስ፣ወደ ተራሮችም የሚጮኽበት ቀን አለው።

6. ኤላም የፍላጻ ሰገባ፣ፈረሷንና ሠረገላዋን አዘጋጀች፤ቂርም ጋሻዋን አነገበች

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 22