ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 14:14-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. ከደመናዎችም ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፤ራሴንም እንደ ልዑል አደርጋለሁ።”

15. ነገር ግን ወደ ሲኦል፣ወደ ጥልቁም ጒድጓድ ወርደሃል።

16. የሚያዩህም አትኵረው እየተመለክቱህ፣በመገረም ስለ አንተ እንዲህ ይላሉ፤“ያ ምድርን ያናወጠ፣መንግሥታትን ያንቀጠቀጠ፣ ይህ ሰው ነውን?

17. ዓለምን ምድረ በዳ ያደረገ፤ከተሞችን ያፈራረሰ፣ምርኮኞቹንም ወደ አገራቸው እንዳይሄዱ የከለከለ ይህ ነውን?”

18. የአሕዛብ ነገሥታት ሁሉ በክብር አንቀላፍተዋል፤በየመቃብራቸው ዐርፈዋል።

19. አንተ ግን እንደማይፈለግ ቅርንጫፍ፣ከመቃብር ወጥተህ ተጥለሃል፤በሰይፍ በተወጉት፣ወደ ጥልቁ ድንጋዮች በወረዱት፣በተገደሉትም ተሸፍነሃል።እንደ ተረገጠም ሬሳ ሆነሃል።

20. ከእነርሱ ጋር በመቃብር አትሆንም፤ምድርህን አጥፍተሃልና፤ሕዝብህንም ፈጅተሃልና።የክፉ አድራጊዎች ዘርፈጽሞ አይታወስም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 14