ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 10:7-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. እርሱ ግን እንዲህ አላሰበም፤በልቡም ይህ አልነበረም፤ነገር ግን ዕቅዱ ለማጥፋት፣ብዙ ሕዝቦችንም ለመደምሰስ ነበር።

8. እንዲህም ይል ነበር፤‘የጦር አዛዦቼ በሙሉ ነገሥታት አይደሉምን?

9. ካልኖ እንደ ከርከሚሽ፣ሐማት እንደ አርፋድ፣ሰማርያስ እንደ ደማስቆ አይደሉምን?

10. የጣዖታትን መንግሥታት፣ምስሎቻቸው ከኢየሩሳሌምና ከሰማርያ መንግሥታት የሚበልጡትን እጄ እንደ ያዘች ሁሉ፣

11. በሰማርያና በጣዖቶቿ ያደረግሁትን፣በኢየሩሳሌምና በተቀረጹ ምስሎቿስ እንዲሁ አላደርግምን?።”

12. ጌታ በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም ላይ የሚያደርገውን ሁሉ ከፈጸመ በኋላ፣ እንዲህ ይላል የአሦርን ንጉሥ ስለ ልቡ ትዕቢትና ስለ ንቀት አመለካከቱ እቀጣዋለሁ፤

13. የአሦር ንጉሥ እንዲህ ይላልና፤“ ‘ይህን ሁሉ ያደረግሁት በክንዴ ብርታት ነው፤ደግሞም በጥበቤ አስተዋይ ነኝና።የመንግሥታትን ድንበር አፈረስሁ፤ሀብታቸውን ዘረፍሁ፤ነገሥታታቸውን እንደ አንድ ኀያል ሆኜ አዋረድሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 10