ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 10:6-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ሀብታቸውን እንዲዘርፍ፣ ምርኮን እንዲያግበሰብስ፣እንደ መንገድ ላይ ጭቃም እንዲረግጣቸው፣አምላክ በሌለው ሕዝብ ላይ እልከዋለሁ፣በሚያስቈጣኝም ሕዝብ ላይ እሰደዋለሁ።

7. እርሱ ግን እንዲህ አላሰበም፤በልቡም ይህ አልነበረም፤ነገር ግን ዕቅዱ ለማጥፋት፣ብዙ ሕዝቦችንም ለመደምሰስ ነበር።

8. እንዲህም ይል ነበር፤‘የጦር አዛዦቼ በሙሉ ነገሥታት አይደሉምን?

9. ካልኖ እንደ ከርከሚሽ፣ሐማት እንደ አርፋድ፣ሰማርያስ እንደ ደማስቆ አይደሉምን?

10. የጣዖታትን መንግሥታት፣ምስሎቻቸው ከኢየሩሳሌምና ከሰማርያ መንግሥታት የሚበልጡትን እጄ እንደ ያዘች ሁሉ፣

11. በሰማርያና በጣዖቶቿ ያደረግሁትን፣በኢየሩሳሌምና በተቀረጹ ምስሎቿስ እንዲሁ አላደርግምን?።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 10