ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

አሞጽ 4:8-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ሰዎች ውሃ ፍለጋ ከከተማ ወደ ከተማ ባዘኑ፣ይሁን እንጂ ጠጥተው አልረኩም፤እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም፤”ይላል እግዚአብሔር።

9. “የአትክልትና የወይን ቦታዎቻችሁን ብዙ ጊዜ መታሁ፤በዋግና በአረማሞም አጠፋኋቸው፤አንበጦችም የበለስና የወይራ ዛፎቻችሁን በሉ፤እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም፤”ይላል እግዚአብሔር።

10. “በግብፅ ላይ እንዳደረግሁት፣መቅሠፍትን ላክሁባችሁ፤ከተማረኩት ፈረሶቻችሁ ጋር፣ጐልማሶቻችሁን በሰይፍ ገደልሁ፤የሰፈራችሁ ግማት አፍንጫችሁ እንዲገባ አደረግሁ፤እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም”ይላል እግዚአብሔር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ አሞጽ 4