ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሶፎንያስ 3:9-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. “በዚያ ጊዜ ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሔርን ስም እንዲጠሩ፣ተስማምተው እንዲያገለግሉት፣አንደበታቸውን አጠራለሁ።

10. ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ፣የሚያመልኩኝ፣ የተበተኑት ሕዝቤቊርባን ያመጡልኛል።

11. በእኔ ላይ ከፈጸማችሁት በደል ሁሉ የተነሣ፣በዚያ ቀን አታፍሩም፤በትዕቢታቸው የሚደሰቱትን፣ከዚህች ከተማ አስወግዳለሁና፤ከእንግዲህ ወዲያ፣በቅዱስ ተራራዬ ላይ አትታበዩብኝም።

12. በእግዚአብሔር ስም የሚታመኑትን፣የዋሃንንና ትሑታንን፣በመካከላችሁ አስቀራለሁ።

13. የእስራኤል ትሩፋን ኀጢአት አይሠሩም፤ሐሰትም አይናገሩም፤በአንደበታቸውም ተንኰል አይገኝም።ይበላሉ፤ ይተኛሉ፤የሚያስፈራቸውም የለም።

14. የጽዮን ልጅ ሆይ፤ ዘምሪ፤እስራኤል ሆይ፤ እልል በይ፤የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፤በፍጹም ልብሽ ደስ ይበልሽ፤ ሐሤትም አድርጊ።

15. እግዚአብሔር ቅጣትሽን አስወግዶታል፤ጠላቶችሽን ከአንቺ መልሶአል፤የእስራኤል ንጉሥ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው፤ከእንግዲህ ወዲያ አንዳች ክፉ ነገር አትፈሪም።

16. በዚያ ቀን ኢየሩሳሌምን እንዲህይሏታል፤“ጽዮን ሆይ፤ አትፍሪ፤እጆችሽም አይዛሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሶፎንያስ 3