ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሰቆቃወ 5:11-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. ሴቶች በጽዮን፣ደናግል በይሁዳ ከተሞች ተደፈሩ።

12. መሳፍንት በእነርሱ እጅ ተሰቀሉ፤ሽማግሌዎችም አልተከበሩም።

13. ጐልማሶች ወፍጮ እንዲፈጩ ተገደዱ፤ወንዶች ልጆች በዕንጨት ሸክም ተንገዳገዱ።

14. ሽማግሌዎች ከከተማዪቱ በር ሄደዋል፤ጐልማሶች ዝማሬያቸውን አቁመዋል።

15. ደስታ ከልባችን ጠፍቶአል፤ጭፈራችን ወደ ልቅሶ ተለውጦአል።

16. አክሊላችን ከራሳችን ላይ ወድቆአል፤ወዮልን፤ ኀጢአት ሠርተናልና!

17. ከዚህ የተነሣ ልባችን ደከመ፤ከእነዚህ የተነሣም ዐይናችን ፈዘዘ፤

18. ባዶዋን የቀረችው የጽዮን ተራራ፣የቀበሮዎች መፈንጫ ሆናለችና።

19. አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ለዘላለም ትገዛለህ፤ዙፋንህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል።

20. ስለ ምን ፈጽመህ ትረሳናለህ?ስለምንስ ለረዥም ጊዜ ትተወናለህ?

21. እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ መልሰን፤ እኛም እንመለሳለን፤ዘመናችንን እንደ ቀድሞው አድስ፤

22. ፈጽመህ ካልጣልኸን፣ከመጠን በላይ ካልተቈጣኸን።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሰቆቃወ 5