ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሰቆቃወ 3:46-64 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

46. “ጠላቶቻችን ሁሉ፣አፋቸውን በእኛ ላይ ከፈቱ።

47. በጥፋትና በመፈራረስ፣በችግርና በሽብር ተሠቃየን።

48. የእንባ ጐርፍ ከዐይኔ ፈሰሰ፤ሕዝቤ አልቋልና።

49. ያለ ዕረፍት፣ያለ ማቋረጥ ዐይኖቼ እንባ ያፈሳሉ፤

50. እግዚአብሔር ከላይ፣ከሰማይ እስኪያይ ድረስ።

51. በከተማዬ ባሉት ሴቶች ሁሉ ላይ የደረሰውን ማየቴ፣ነፍሴን አስጨነቃት።

52. ያለ ምክንያት ጠላቶቼ የሆኑ፣እንደ ወፍ አደኑኝ።

53. ሕይወቴን በጒድጓድ ውስጥ ሊያጠፉ ሞከሩ፣ድንጋይም በላዬ አደረጉ።

54. ውሃ ሞልቶ በዐናቴ ላይ ፈሰሰ፤ጠፍቻለሁ ብዬ አሰብሁ።

55. በጥልቁ ጒድጓድ ውስጥ ሳለሁ፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ የአንተን ስም ጠራሁ።

56. ልመናዬን ሰምተሃል፤ “ርዳታም ፈልጌ ስጮኽ፣ከመስማት ጆሮህን አትከልክል።”

57. በጠራሁህ ጊዜ ቀረብኸኝ፣እንዲሁም፣ “አትፍራ” አልኸኝ።

58. ጌታ ሆይ፤ ለእኔ ተሟገትኽልኝ፤ሕይወቴንም ተቤዠህ።

59. እግዚአብሔር ሆይ፤ በእኔ ላይ የተደረገውን ግፍ አየህ፤ፍርዴን ፍረድልኝ!

60. በቀላቸውን ሁሉ፣በእኔም ላይ ያሰቡትን ዐድማ አየህ።

61. እግዚአብሔር ሆይ፤ ስድባቸውን ሁሉ፣በእኔ ላይ ያሰቡትን ዐድማ ሁሉ ሰማህ፤

62. ይህም ቀኑን ሙሉ በእኔ ላይ፣ጠላቶቼ የሚያውጠነጥኑትና የሚያንሾካሹኩት ነው።

63. ተመልከታቸው! ቆመውም ሆነ ተቀምጠው፣በዘፈናቸው ይሣለቁብኛል።

64. እግዚአብሔር ሆይ፤ እጆቻቸው ላደረጉት፣የሚገባውን መልሰህ ክፈላቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሰቆቃወ 3