23. ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ታማኝነትህም ብዙ ነው።
24. ራሴን እንዲህ አልሁት፤ “እግዚአብሔር ዕድል ፈንታዬ ነው፤ስለዚህ ተስፋ አደርገዋለሁ።
25. እርሱን ተስፋ ለሚያደርጉት፣ለሚፈልገውም ሰው እግዚአብሔር መልካም ነው።
26. ሰው የእግዚአብሔርን ማዳን፣ዝም ብሎ ተስፋ ቢያደርግ መልካም ነው።
27. ሰው በወጣትነቱ፣ቀንበር ቢሸከም መልካም ነው።
28. ብቻውን ዝም ብሎ ይቀመጥ፤ እግዚአብሔር አሸክሞታልና።