1. በቊጣው በትር፣መከራ ያየ ሰው እኔ ነኝ።
2. ከፊቱ አስወጣኝ፤በብርሃን ሳይሆን በጨለማ እንድሄድ አደረገኝ።
3. በእርግጥ ቀኑን ሁሉ በመደጋገም፣እጁን በላዬ ላይ መለሰ።
4. እርሱ ሥጋዬንና ቈዳዬን አስረጀ፤ዐጥንቶቼንም ሰባበረ።
5. በምሬትና በድካም፣ቅጥር ሠራብኝ፤ ዙሪያዬንም ከበበኝ።
6. ከሞቱ ብዙ ጊዜ እንደሆናቸው፣በጨለማ እንድኖር አደረገኝ።
7. በቅጥር ውስጥ ዘጋብኝ፤ ስለዚህ ማምለጥ አልቻልሁም፤የእስር ሰንሰለቴንም አከበደብኝ።