ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሰቆቃወ 1:9-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. ርኵሰቷ በቀሚሷ ላይ ታየ፤ ወደ ፊት የሚሆንባትን አላሰበችም፤አወዳደቋ አስደንጋጭ ሆነ፤የሚያጽናናትም አልነበረም፤“እግዚአብሔር ሆይ፤ መከራዬንተመልከት፤ጠላት ድል አድርጎአልና!”

10. በሀብቷ ሁሉ ላይ፣ጠላት እጁን ዘረጋ፤ወደ ጉባኤህ እንዳይገቡ፣የከለከልሀቸው፣ጣዖት የሚያመልኩ አሕዛብ፣ወደ መቅደሷ ሲገቡ አየች።

11. እንጀራ በመፈለግ፣ሕዝቧ ሁሉ በሥቃይ ይጮኻል፤በሕይወት ለመኖር፣የከበረ ሀብታቸውን በምግብ ይለውጣሉ፤“አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ አስበኝ፤ ተመልከተኝም፤እኔ ተዋርጃለሁና።”

12. “እናንት መንገድ ዐላፊዎች ሁሉ፤ ይህ ለእናንተ ምንም አይደለምን?ተመልከቱ፤ እዩም፤በጽኑ ቍጣው ቀን፣ እግዚአብሔር ያመጣብኝን፣በእኔ ላይ የደረሰውን፣የእኔን መከራ የመሰለ መከራ አለን?

13. “ከከፍታ ስፍራ እሳትን ላከ፤ወደ ታች ወደ ዐጥንቶቼም ሰደደው፤በእግሮቼ ላይ መረብ ዘረጋ፤ወደ ኋላም ጣለኝ፤ቀኑን ሙሉ በማድከም፣ባዶ አድርጎ አስቀመጠኝ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሰቆቃወ 1