ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 7:8-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. የቤቷን አቅጣጫ ይዞ፣በቤቷ ማእዘን አጠገብ ባለው መንገድ ያልፍ ነበር፤

9. ቀኑ መሸትሸት ሲል፣በውድቅት ሌሊት፣ በጽኑ ጨለማ።

10. ከዚያም አንዲት ሴት ልታገኘው ወጣች፤እንደ ዝሙት አዳሪ ለብሳ፣ ለማሳሳት ታጥቃ።

11. ጯኺና ማን አለብኝ ባይ ናት፤እግሮቿ አርፈው ቤት አይቀመጡም፤

12. አንዴ በመንገድ፣ አንዴ በአደባባይ፤በየማእዘኑም ታደባለች።

13. አፈፍ አድርጋ ይዛ ሳመችው፤ኀፍረቷንም ጥላ እንዲህ አለችው፤

14. “በቤቴ የኅብረት መሥዋዕት ማቅረብ ነበረብኝ፤ዛሬ ስእለቴን ፈጸምሁ፤

15. ስለዚህ አንተን ለማግኘት ወጣሁ፤ፈልጌህ ነበር፤ ይኸው አገኘሁህ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 7