ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 7:16-23 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. ዐልጋዬን ከግብፅ የመጣ፣ጌጠኛ በፍታ አልብሼዋለሁ።

17. ዐልጋዬን፣የከርቤ፣ የዓልሙንና የቀረፋ ሽቱ አርከፍክፌበታለሁ።

18. ና፤ እስኪነጋ በጥልቅ ፍቅር እንርካ፤በፍቅር ራሳችንን እናስደስት።

19. ባሌ እቤት የለም፤ሩቅ አገር ሄዷል።

20. በገንዘብ የተሞላ ቦርሳ ወስዷል፤ጨረቃዋ ሙሉ እስክትሆን አይመለስም።”

21. በሚያግባቡ ቃላት አሳተችው፤በለሰለሰ አንደበቷ አታለለችው።

22. ለዕርድ እንደሚነዳ በሬ፣ወደ ወጥመድ እንደሚገባ አጋዘን፣ሳያንገራግር ተከተላት፤

23. ፍላጻ ጒበቱን እስኪወጋው ድረስ፣ሕይወቱን እንደሚያሳጣው ሳያውቅ፣በራ ወደ ወጥመድ እንደምትገባ ወፍ ሆነ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 7