ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 7:11-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. ጯኺና ማን አለብኝ ባይ ናት፤እግሮቿ አርፈው ቤት አይቀመጡም፤

12. አንዴ በመንገድ፣ አንዴ በአደባባይ፤በየማእዘኑም ታደባለች።

13. አፈፍ አድርጋ ይዛ ሳመችው፤ኀፍረቷንም ጥላ እንዲህ አለችው፤

14. “በቤቴ የኅብረት መሥዋዕት ማቅረብ ነበረብኝ፤ዛሬ ስእለቴን ፈጸምሁ፤

15. ስለዚህ አንተን ለማግኘት ወጣሁ፤ፈልጌህ ነበር፤ ይኸው አገኘሁህ።

16. ዐልጋዬን ከግብፅ የመጣ፣ጌጠኛ በፍታ አልብሼዋለሁ።

17. ዐልጋዬን፣የከርቤ፣ የዓልሙንና የቀረፋ ሽቱ አርከፍክፌበታለሁ።

18. ና፤ እስኪነጋ በጥልቅ ፍቅር እንርካ፤በፍቅር ራሳችንን እናስደስት።

19. ባሌ እቤት የለም፤ሩቅ አገር ሄዷል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 7