ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 30:4-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. ወደ ሰማይ የወጣ፣ የወረደስ ማነው?ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ ማነው?ውሆችንስ በመጐናጸፊያው የጠቀለለ ማነው?የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ ማነው?ስሙ ማን ነው? የልጁስ ስም ማን ይባላል?የምታውቅ ከሆነ እስቲ ንገረኝ!

5. “የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንከን የለበትም፤እርሱ ለሚታመኑበት ሁሉ ጋሻቸው ነው።

6. በእርሱ ቃል ላይ አንዳች አትጨምር፤አለዚያ ይዘልፍሃል፤ ሐሰተኛም ያደርግሃል።

7. “እግዚአብሔር ሆይ፤ ሁለት ነገር እለምንሃለሁ፤እነዚህንም ከመሞቴ በፊት አትከልክለኝ፤

8. ሐሰትንና ሐሰት መናገርን ከእኔ አርቅልኝ፤ድኽነትንም ሆነ ብልጽግናን አትስጠኝ፤ብቻ የዕለት እንጀራዬን ስጠኝ።

9. ያለዚያ ግን ያለ ልክ እጠግብና እክድሃለሁ፤‘እግዚአብሔር ማን ነው?’ እላለሁ፤ወይም ድኻ እሆንና እሰርቃለሁ፤የአምላኬንም ስም አሰድባለሁ።

10. “አገልጋይን በጌታው ፊት በክፉ አታንሣው፤አለዚያ ይረግምህና ጒዳት ያገኝሃል።

11. “አባቱን የሚረግም፣እናቱን የማይባርክ ትውልድ አለ፤

12. ራሳቸውን ንጹሓን አድርገው የሚቈጥሩ፣ሆኖም ከርኵሰታቸው ያልነጹ አሉ፤

13. ዐይናቸው ትዕቢተኛ የሆነ፣ አስተያያቸው ንቀት የሞላበት፣

14. ድኾችን ከምድር፣ችግረኞችንም ከሰው ዘር መካከል ለማጥፋት፣ጥርሳቸው ሰይፍ የሆነ፣መንጋጋቸውም ካራ የሆነ አሉ።

15. “አልቅት ሁለት ሴት ልጆች አሉት፤‘ስጡን! ስጡን!’ እያሉ ይጮኻሉ፤“ፈጽሞ የማይጠግቡ ሦስት ነገሮች አሉ፤‘በቃኝን’ ከቶ የማያውቁ አራት ናቸው፤

16. እነርሱም መቃብር፣ መካን ማሕፀን፣ውሃ ጠጥታ የማትረካ ምድር፣‘በቃኝ’ የማይል እሳት ናቸው።

17. “በአባት ላይ የምታፌዝ ዐይን፣የእናትንም ትእዛዝ የምትንቅ፣የሸለቆ ቊራዎች ይጐጠጒጧታል፤ጆፌ አሞሮችም ይበሏታል።

18. “እጅግ የሚያስደንቁኝ ሦስት ነገሮች አሉ፤የማላስተውላቸውም አራት ናቸው፤

19. የንስር መንገድ በሰማይ፣የእባብ መንገድ በቋጥኝ፣የመርከብ መንገድ በባሕር፣የሰውም መንገድ ከሴት ልጅ ጋር ናቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 30