ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 29:10-23 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ደም የተጠሙ ሰዎች ሐቀኛን ሰው ይጠላሉ፤ቅን የሆነውንም ለመግደል ይሻሉ።

11. ተላላ ሰው ቊጣውን ያለ ገደብ ይለቀዋል፤ጠቢብ ሰው ግን ራሱን ይቈጣጠራል።

12. ገዥ የሐሰት ወሬ የሚሰማ ከሆነ፣ሹማምቱ ሁሉ ክፉዎች ይሆናሉ።

13. ድኻውና ጨቋኙ የጋራ ነገር አላቸው፤ እግዚአብሔር ለሁለቱም የዐይን ብርሃንን ሰጥቶአቸዋል።

14. ንጉሥ ለድኻ ትክክለኛ ፍርድ ቢሰጥ፣ዙፋኑ ዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

15. የተግሣጽ በትር ጥበብን ታጐናጽፋለች፤መረን የተለቀቀ ልጅ ግን እናቱን ያሳፍራል።

16. ክፉዎች ሥልጣን ሲይዙ ኀጢአት ይበዛል፤ጻድቃን ግን የእነርሱን ውድቀት ያያሉ።

17. ልጅህን ቅጣው፤ ሰላም ይሰጥሃል፤ነፍስህንም ደስ ያሰኛታል።

18. ራእይ በሌለበት ሕዝብ መረን ይሆናል፤ሕግን የሚጠብቅ ግን የተባረከ ነው።

19. አገልጋይ በቃል ብቻ ሊታረም አይችልም፤ቢያስተውለውም እንኳ በጀ አይልም።

20. በችኰላ የሚናገርን ሰው ታያለህን?ከእርሱ ይልቅ ተላላ ተስፋ አለው።

21. ሰው አገልጋዩን ከልጅነቱ ጀምሮ ቢያቀማጥል፣የኋላ ኋላ ሐዘን ያገኘዋል።

22. ቊጡ ሰው ጠብን ይጭራል፤ግልፍተኛም ብዙ ኀጢአት ይሠራል።

23. ሰውን ትዕቢቱ ያዋርደዋል፤ ትሑት መንፈስ ያለው ግን ክብርንይጐናጸፋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 29