ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 28:8-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. በከፍተኛ ወለድ ሀብቱን የሚያካብት፣ለድኻ ለሚራራ፣ ለሌላው ሰው ያከማችለታል።

9. ሕግን ላለመስማት ጆሮውን የሚደፍን፣ጸሎቱ እንኳ አስጸያፊ ነው።

10. ቅኖችን በክፉ መንገድ የሚመራ፣በቈፈረው ጒድጓድ ይገባል፤ንጹሓን ግን መልካም ነገርን ይወርሳሉ።

11. ባለጠጋ ራሱን ጠቢብ አድርጎ ይቈጥር ይሆናል፤አስተዋይ የሆነ ድኻ ግን መርምሮ ያውቀዋል።

12. ጻድቃን ድል ሲነሡ ታላቅ ደስታ ይሆናል፤ክፉዎች ሥልጣን ሲይዙ ግን ሕዝብ ይሸሸጋል።

13. ኀጢአቱን የሚሰውር አይለማም፤የሚናዘዝና የሚተወው ግን ምሕረትን ያገኛል።

14. እግዚአብሔርን ዘወትር የሚፈራ ሰው ቡሩክ ነው፤ልቡን የሚያደነድን ግን መከራ ላይ ይወድቃል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 28