ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 28:21-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

21. አድልዎ ማድረግ መልካም አይደለም፤ሰው ግን ለቊራሽ እንጀራ ሲል በደል ይፈጽማል።

22. ስስታም ሀብት ለማከማቸት ይስገበገባል፤ድኽነት እንደሚጠብቀውም አያውቅም።

23. ሸንጋይ አንደበት ካለው ይልቅ፣ሰውን የሚገሥጽ ውሎ ዐድሮ ይወደዳል።

24. ከአባት ከእናቱ ሰርቆ፣“ይህ ጥፋት አይደለም” የሚል የአጥፊ ተባባሪ ነው።

25. ስስታም ሰው ጠብን ያነሣሣል፤ በእግዚአብሔር የሚታመን ግን ይባረካል።

26. በራሱ የሚታመን ተላላ ነው፤በጥበብ የሚመላለስ ግን ክፉ አያገኘውም።

27. ለድኾች የሚሰጥ አይቸገርም፤አይቶአቸው እንዳላየ የሚሆን ግን ብዙ ርግማን ይደርስበታል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 28