ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 28:16-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. ጨካኝ ገዥ ማመዛዘን ይጐድለዋል፤ያላግባብ የሚገኝን ጥቅም የሚጸየፍ ግን ዕድሜው ይረዝማል።

17. የሰው ደም ያለበት ሰው፣ዕድሜ ልኩን ሲቅበዘበዝ ይኖራል፤ማንም ሰው አይርዳው።

18. አካሄዱ ነቀፋ የሌለበት ሰው ክፉ አያገኘውም፤መንገዱ ጠማማ የሆነ ግን ድንገት ይወድቃል።

19. መሬቱን የሚያርስ የተትረፈረፈ ምግብ ያገኛል፤ከንቱ ተስፋን ይዞ የሚጓዝ ግን ድኽነትን ይወርሳል።

20. ታማኝ ሰው እጅግ ይባረካል፤ሀብት ለማግኘት የሚጣደፍ ግን ከቅጣት አያመልጥም።

21. አድልዎ ማድረግ መልካም አይደለም፤ሰው ግን ለቊራሽ እንጀራ ሲል በደል ይፈጽማል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 28