ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 16:1-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. የልብ ዕቅድ የሰው ነው፤የአንደበት መልስ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

2. ለሰው መንገዱ ሁሉ ንጹሕ መስሎ ይታየዋል፤መነሻ ሐሳቡ ግን በእግዚአብሔር ይመዘናል።

3. የምታደርገውን ሁሉ ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ፤ዕቅድህም ሁሉ ይሳካልሃል።

4. እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር ለራሱ ዐላማ ሠርቶአል፤ክፉዎችንም እንኳ ለጥፋት ቀን አዘጋጅቶአል።

5. እግዚአብሔር በልብ የሚታበዩትን ሁሉ ይጸየፋል፤እነርሱም ከቅጣት እንደማያመልጡ በርግጥ ዕወቅ።

6. በፍቅርና በታማኝነት ኀጢአት ይሰረያል፤ እግዚአብሔርን በመፍራት ሰው ከክፋት ይርቃል።

7. የሰው መንገድ እግዚአብሔርን ደስ ሲያሰኘው፣ጠላቶቹ እንኳ አብረውት በሰላም እንዲኖሩ ያደርጋል።

8. ከጽድቅ ጋር ጥቂቱ ነገር፣በግፍ ከሚገኝ ብዙ ትርፍ ይሻላል።

9. ሰው በልቡ መንገዱን ያቅዳል፤ እግዚአብሔር ግን ርምጃውን ይወስንለታል።

10. የንጉሥ ከንፈሮች እንደ አምላክ ቃል ይናገራሉ፤አንደበቱ ፍትሕን ያዛባ ዘንድ አይገባም።

11. ሐቀኛ መስፈሪያና ሚዛን ከእግዚአብሔር ናቸው፤በከረጢት ውስጥ ያሉት መመዘኛዎችም ሁሉ ሥራዎቹ ናቸው።

12. ክፋትን ማድረግ ለነገሥታት አጸያፊ ነው፤ዙፋን የሚጸናው በጽድቅ ነውና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 16