ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 11:7-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ክፉ ሰው ሲሞት ተስፋው ከንቱ ትሆናለች፤በኀይሉ የተመካበትም ሁሉ እንዳልነበረ ይሆናል።

8. ጻድቅ ከመከራ ይድናል፤ይልቁን መከራው በክፉው ላይ ይደርሳል።

9. ክፉ ሰው ባልንጀራውን በአፉ ያጠፋል፤ጻድቃን ግን በዕውቀት ያመልጣሉ።

10. ጻድቃን ሲሳካላቸው ከተማ ደስ ይላታል፤ክፉዎች ሲጠፉ እልልታ ይሆናል።

11. በቅኖች በረከት ከተማ ከፍ ከፍ ትላለች፤በክፉዎች አንደበት ግን ትጠፋለች።

12. ማመዛዘን የጐደለው ሰው ባልንጀራውን ያንኳስሳል፤አስተዋይ ግን አንደበቱን ይገዛል።

13. ሐሜተኛ ምስጢር አይጠብቅም፤ታማኝ ሰው ግን ምስጢር ይጠብቃል።

14. በአመራር ጒድለት መንግሥት ይወድቃል፤የመካሮች ብዛት ግን ድልን ርግጠኛ ያደርጋል።

15. ለማይታወቅ ሰው ዋስ የሚሆን መከራ ያገኘዋል፤ዋስትና ለመስጠት እጅ የማይመታ ግን ምንም አይደርስበትም።

16. ርኅሩኅ ሴት ክብር ታገኛለች፤ጒልበተኛ ሰዎች ግን ብልጽግናን ብቻ ያገኛሉ።

17. ደግ ሰው ራሱን ይጠቅማል፤ጨካኝ ግን በራሱ ላይ መከራ ያመጣል።

18. ክፉ ሰው የሚያገኘው ትርፍ መቅኖ የለውም፤ጽድቅን የሚዘራ ግን አስተማማኝ ዋጋ ያገኛል።

19. እውነተኛ ጻድቅ ሕይወትን ያገኛል፤ክፋትን የሚከተል ግን ወደ ሞቱ ይጓዛል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 11