ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 11:20-30 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. እግዚአብሔር ልበ ጠማሞችን ይጸየፋል፤በመንገዳቸው ነቀፋ በሌለባቸው ሰዎች ግን ደስ ይሰኛል።

21. ክፉ ሳይቀጣ እንደማይቀር ዕወቅ፣ጻድቃን ግን በነጻ ይሄዳሉ።

22. በእርያ አፍንጫ ላይ እንደ ተሰካ የወርቅ ቀለበት፣ማስተዋል የጐደላት ቆንጆ ሴት እንዲሁ ናት።

23. የጻድቃን ምኞት ምንጊዜም ፍጻሜው ያማረ ነው፤የክፉዎች ተስፋ ግን በቊጣ ያከትማል።

24. አንዱ በለጋስነት ይሰጣል፤ ሆኖም ይበልጥ ያገኛል፤ሌላው ያለ መጠን ይሰስታል፤ ግን ይደኸያል።

25. ለጋስ ይበለጽጋል፤ሌሎችን የሚያረካም ራሱ ይረካል።

26. በድብቅ እህል የሚያከማቸውን ሕዝብ ይረግመዋል፤አውጥቶ የሚሸጥ ግን በረከት ይጐናጸፋል።

27. በጎ ነገርን ተግቶ የሚሻ በጎ ነገር ይጠብቀዋል፤ክፉ ነገር የሚፈልገውን ግን ክፉ ያገኘዋል።

28. በሀብቱ የሚታመን ሁሉ ይወድቃል፤ጻድቃን ግን እንደ አረንጓዴ ቅጠል ይለመልማሉ።

29. ቤተ ሰቡን የሚያውክ ሰው ነፋስን ይወርሳል፤ተላላም ሰው የጠቢብ ሎሌ ይሆናል።

30. የጻድቅ ፍሬ የሕይወት ዛፍ ናት፤ነፍሳትን የሚማርክም ጠቢብ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 11