ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 11:1-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር የተጭበረበረ ሚዛንን ይጸየፋል፤ትክክለኛ መለኪያ ግን ደስ ያሰኘዋል።

2. ትዕቢት ስትመጣ ውርደትም ትከተላለች፤በትሑት ዘንድ ግን ጥበብ ትገኛለች።

3. ቅኖችን ትክክለኛነታቸው ትመራቸዋለች፤ወስላቶች ግን በገዛ አታላይነታቸው ይጠፋሉ።

4. በቊጣ ቀን ሀብት ፋይዳ የለውም፤ጽድቅ ግን ከሞት ትታደጋለች።

5. ለፍጹማን ሰዎች ጽድቃቸው መንገዳቸውን ታቃናላቸዋለች፤ክፉዎች ግን በገዛ ክፋታቸው ይወድቃሉ።

6. ቅኖችን ጽድቃቸው ትታደጋቸዋለች፤ወስላቶች ግን በክፉ ምኞታቸው ይጠመዳሉ።

7. ክፉ ሰው ሲሞት ተስፋው ከንቱ ትሆናለች፤በኀይሉ የተመካበትም ሁሉ እንዳልነበረ ይሆናል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 11