ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 10:18-25 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

18. ጥላቻውን የሚሸሽግ ሐሰተኛ አንደበት ያለው ነው፤ሐሜትን የሚዘራ ሁሉ ተላላ ነው።

19. ከቃላት ብዛት ኀጢአት አይታጣም፤አንደበቱን የሚገታ ግን ጠቢብ ነው።

20. የጻድቅ አንደበት የነጠረ ብር ነው፤የክፉ ሰው ልብ ግን ርባና የለውም።

21. የጻድቃን ከንፈሮች ብዙዎችን ያንጻሉ፤ተላሎች ግን ከማመዛዘን ጒድለት ይሞታሉ።

22. የእግዚአብሔር በረከት ብልጽግናን ታመጣለች፤መከራንም አያክልባትም።

23. ተላላ ሰው በክፉ ተግባር ይደሰታል፤አስተዋይ ሰው ግን በጥበብ ደስ ይለዋል።

24. ክፉ ሰው የፈራው ይደርስበታል፤ጻድቅ የሚመኘው ይፈጸምለታል።

25. ዐውሎ ነፋስ ሲነሣ ክፉዎች ተጠራርገው ይወሰዳሉ፤ጻድቃን ግን ለዘላለም ጸንተው ይኖራሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 10