ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ማሕልየ መሓልይ 8:6-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. በልብህ እንዳለ፣በክንድህም እንደምትይዘው ማኅተም አስቀምጠኝ፤ፍቅር እንደ ሞት የበረታች፣ቅናቷም እንደ መቃብር ጨካኝ ናትና፤እንደሚንቦገቦግ እሳት፣እንደ ኀይለኛም ነበልባል ትነዳለች።

7. የውሃ ብዛት ፍቅርን ሊያጠፋ አይችልም፣ፈሳሾችም አያሰጥሟትም፤ሰው የቤቱን ሀብት ሁሉስለ ፍቅር ቢሰጥፈጽሞ ይናቃል።

8. ትንሽ እኅት አለችን፤ጡትም ገና አላወጣችም፤ስለ እርሷ በምንጠየቅበት ቀንምን ማድረግ እንችል ይሆን?

9. እርሷ ቅጥር ብትሆን፣በላይዋ የብር መጠበቂያ ማማ እንሠራባታለን፤በር ብትሆን፣በዝግባ ዕንጨት እንከልላታለን።

10. እነሆ እኔ ቅጥር ነኝ፤ጡቶቼም እንደ ማማ ግንቦች ናቸው፤እኔም በዐይኖቹ ፊት፣ሰላምን እንደሚያመጣ ሰው ሆንሁ።

11. ሰሎሞን በብኤላሞን የወይን ተክል ቦታ ነበረው፤የወይኑን ተክል ቦታም ለአትክልተኞች አከራየው፤እያንዳንዳቸውም የፍሬውን ዋጋ፣አንድ አንድ ሺህ ሰቅል ብር ያመጡለት ነበር።

12. የወይኔ ተክል ቦታ የራሴ፣ የግሌ ነው፤ሰሎሞን ሆይ፤ አንድ ሺሁ ሰቅል ለአንተ፤ፍሬውን ለሚጠብቁ ደግም ሁለት መቶ ይሁን።

13. አንቺ በአትክልቱ ቦታ የምትኖሪ ሆይ፤ባልንጀሮቼ ድምፅሽን ይሰማሉ፤እስቲ እኔም ልስማው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ማሕልየ መሓልይ 8