ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ማሕልየ መሓልይ 5:1-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እኅቴ ሙሽራዬ፣ ወደ አትክልት ቦታዬ መጥቻለሁ፤ከርቤዬን ከቅመሜ ጋር ሰብስቤአለሁ፤የማር እንጀራዬን ከነወለላው በልቻለሁ፤ወይኔንና ወተቴንም ጠጥቻለሁ።ወዳጆች ሆይ፤ ብሉ፤ ጠጡ፤እናንት ፍቅረኞች ሆይ፤ እስክትረኩ ጠጡ።

2. እኔ ተኝቻለሁ፤ ልቤ ግን ነቅቶአል፤ስሙ! ውዴ በር ያንኳኳል፤ እንዲህ ይላል፤“እኅቴ ወዳጄ፣ ርግቤ፣አንቺ እንከን የሌለብሽ፤ ክፈቺልኝ፤ራሴ በጤዛ፣ጠጒሬም በሌሊቱ ርጥበት ረስርሶአል።”

3. ቀሚሴን አውልቄአለሁ፤ታዲያ እንዴት እንደ ገና ልልበስ?እግሬን ታጥቤአለሁ፤እንዴት እንደ ገና ላቈሽሸው?

4. ውዴ እጁን በበሩ ቀዳዳ አሾለከ፤ልቤም ስለ እርሱ ይታወክ ጀመር።

5. ለውዴ ልከፍትለት ተነሣሁ፤በከርቤ ነጠብጣብ የራሱት እጆቼ፣በከርቤም ፈሳሽ የተነከሩት ጣቶቼ፣የመወርወሪያውን እጀታ ያዙ።

6. ለውዴ ከፈትሁለት፤ውዴ ግን አልነበረም፤ ሄዶአል፤በመሄዱም ልቤ ደነገጠ፤ፈለግሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም፤ጠራሁት፤ ነገር ግን አልመለሰልኝም።

7. የከተማዪቱም ጠባቂዎች፣በከተማዪቱ ውስጥ ሲዘዋወሩ አገኙኝ፤እነዚህ የቅጥሩ ጠባቂዎች፣ደበደቡኝ፤ አቈሰሉኝ፤ልብሴንም ገፈፉኝ።

8. እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፤እማጠናችኋለሁ፤ውዴን ካገኛችሁት፣ምን ትሉት መሰላችሁ?በፍቅሩ መታመሜን ንገሩት።

9. አንቺ ከሴቶች ሁሉ የተዋብሽ ሆይ፤ውድሽ ከሌሎች እንዴት ቢበልጥ ነው?እስከዚህ የምትማጠኚንስ፣ውድሽ ከሌሎች እንዴት ቢበልጥ ነው?

10. ውዴ ፍልቅልቅና ደመ ግቡ ነው፤ከዐሥር ሺሆችም የሚልቅ ነው።

11. ራሱ የጠራ ወርቅ፣ጠጒሩ ዞማ፣እንደ ቊራም የጠቈረ ነው።

12. ዐይኖቹ፣በጅረት አጠገብ እንዳሉ ርግቦች፣በወተት የታጠቡ፣እንደ ዕንቊም ጒብ ጒብ ያሉ ናቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ማሕልየ መሓልይ 5