ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 4:2-5 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. ብዙ አሕዛብ መጥተው እንዲህ ይላሉ፤“ኑ፤ ወደ እግዚአብሔር ተራራ፣ወደ ያዕቆብ አምላክ ቤት እንሂድ፤በመንገዱ እንድንሄድ፣መንገዱን ያስተምረናል።”ሕግ ከጽዮን ይመጣል፤ የእግዚአብሔርም ቃል ከኢየሩሳሌም።

3. እርሱ በብዙ ሕዝብ መካከል ይፈርዳል፤በሩቅና በቅርብ ባሉ ኀያላን መንግሥታት መካከል ያለውን ግጭት ያቆማል፤ሰይፋቸውን ማረሻ፣ጦራቸውንም ማጭድ ያደርጉታል።አንዱ መንግሥት በሌላው መንግሥት ላይ ሰይፍ አያነሣም፤ከእንግዲህም የጦርነት ትምህርት አይማሩም።

4. እያንዳንዱ ሰው በገዛ ወይኑ ሥር፣ከገዛ በለሱም ሥር ይቀመጣል፤የሚያስፈራቸው አይኖርም፤ የእግዚአብሔር ጸባኦት አፍ ተናግሮአልና።

5. አሕዛብ ሁሉ፣በአማልክቶቻቸው ስም ይሄዳሉ፤እኛ ግን በአምላካችን በእግዚአብሔር ስም፣ከዘላለም እስከ ዘላለም እንሄዳለን።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሚክያስ 4