ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 4:1-3 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በመጨረሻው ዘመን፣ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተራራ፣ከተራሮች ልቆ ይታያል፤ከኰረብቶች በላይ ከፍ ይላል፤ሕዝቦችም ወደ እርሱ ይጐርፋሉ።

2. ብዙ አሕዛብ መጥተው እንዲህ ይላሉ፤“ኑ፤ ወደ እግዚአብሔር ተራራ፣ወደ ያዕቆብ አምላክ ቤት እንሂድ፤በመንገዱ እንድንሄድ፣መንገዱን ያስተምረናል።”ሕግ ከጽዮን ይመጣል፤ የእግዚአብሔርም ቃል ከኢየሩሳሌም።

3. እርሱ በብዙ ሕዝብ መካከል ይፈርዳል፤በሩቅና በቅርብ ባሉ ኀያላን መንግሥታት መካከል ያለውን ግጭት ያቆማል፤ሰይፋቸውን ማረሻ፣ጦራቸውንም ማጭድ ያደርጉታል።አንዱ መንግሥት በሌላው መንግሥት ላይ ሰይፍ አያነሣም፤ከእንግዲህም የጦርነት ትምህርት አይማሩም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሚክያስ 4