ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 40:8-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. አምላኬ ሆይ፤ ፈቃድህን ላደርግ እሻለሁ፤ሕግህም በልቤ ውስጥ አለ።”

9. በታላቅ ጉባኤ ውስጥ ጽድቅን አበሠርሁ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ እንደምታውቀው፣ከንፈሮቼን አልገጠምሁም።

10. ጽድቅህን በልቤ አልሸሸግሁም፤ታማኝነትህንና ማዳንህን እናገራለሁ፤ምሕረትህንና እውነትህን፣ከታላቅ ጉባኤ አልደበቅሁም።

11. እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህን አትንፈገኝ፤ቸርነትህና እውነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ፤

12. ስፍር ቍጥር የሌለው ክፋት ከቦኛልና፤የኀጢአቴ ብዛት ስለ ያዘኝ ማየት ተስኖኛል፤ከራሴ ጠጒር ይልቅ በዝቶአል፤ልቤም ከድቶኛል።

13. እግዚአብሔር ሆይ፤ ታድነኝ ዘንድ ፈቃድህ ይሁን፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

14. ነፍሴን ለመንጠቅ የሚፈልጉ፣ይፈሩ፤ ይዋረዱም፤ጒዳቴንም የሚሹ፣ተዋርደው በመጡበት ይመለሱ።

15. በእኔ ላይ፣ “እሰይ! እሰይ!” የሚሉ፣በራሳቸው እፍረት ይደንግጡ።

16. አንተን የሚፈልጉ ሁሉ ግን፣ሐሤት ያድርጉ፤ በአንተም ደስ ይበላቸው፤ዘወትር የአንተን ማዳን የሚወዱ፣ “እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ይበል” ይበሉ።

17. እኔ ድኻና ችግረኛ ነኝ፤ጌታ ግን ያስብልኛል።አንተ ረዳቴና አዳኜ ነህ፤አምላኬ ሆይ፤ አትዘግይ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 40